ህዳር 10 ቀን 2009 ዓ/ም በዩኒቨርሲቲው የስብሰባ ማዕከል በተደረገው የምክክር መድረክ ላይ የአጎራባች ከተሞች የአስተዳደር ሀላፊዎችና የሐገር ሸማግሌዎች የተገኙ ሲሆን በመድረኩ ላይ  በማህበረሰብልማትስራዎችዳይሬክቶሬትና በሐረማያ ሀይቅ ሁለገብ ተፋሰስ ልማት ፕሮጀክት ሥር በ2009 ዓ.ምሊሰሩ የታቀዱ  የልማትስራዎች እንዲሁም በአካባቢው የሚገኙ ሥራ አጥ ወጣቶች ሊሰማሩባቸው በሚችሉ የስራ ዕድሎች ላይ የተደረገ ጥናት ቀርበው በተሰብሳቢዎቹ ውይይት ተድርጎበታል ፡፡

Haramaya University held a discussion with representatives from the local community regarding the activities it planned to carry out during the year

የዩኒቨርሲቲው የማህበረሰብ አገልግሎት ኢንተርፕራይዝ ምክትል ፕሬዝዳንት  ፕሮፌሰር ከበደ ወ/ጻዲቅ የተዘጋጀውን ውይይት አስመልክተው እንደተናገሩት  ዩኒቨርሲቲው የሚሰራቸውን ማህበረሰብ አቀፍ ስራዎች በተመለከተ በተለያዩ መድረኮች ከማህበረሰቡ ጋር ዕቅዶቹን አቅርቦ ውይይት በማድረግና በየደረጃው ማህበረሰቡን በማሳተፍ ወደ ትግበራ እንደሚገባ ገልጸው የዕለቱ ውይይትም በመጀመሪያው ሩብ ዓመት የዝግጅት ምዕራፍ ላይ ለማካሄድ ታስቦ በተለያዩ ምክንያቶች እስካአሁን ቢዘገይም ዕቅዱን ለመተግበር በሂደት ላይ የምንገኝ በመሆኑ ሊሰሩ በታቀዱ ዕቅዶች ላይ ውይይት ተደርጎ በጋራ ወደ ትግበራ ለመግባትና ስኬታማ ስራ ለመስራት እንዲቻል  የውይይቱ መካሄዱ ትልቅ አስተዋጾ እንደሚያደርግ ተናግረዋል፡፡

Haramaya University held a discussion with representatives from the local community regarding the activities it planned to carry out during the year

በውይይቱ ወቅት የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት  ፕሮፌሰር  ጨመዳ ፊኒንሳ እንዳሉት ዩኒቨርሲቲዎች በዋናነት ሶስት ተግባራትን ማለትም የመማር ማስተማር ፣ ጥናትና ምርምር የማካሄድ እንዲሁም  በአካባቢያቸው ለሚገኙ ነዋሪዎች የማህበረሰብ አገልግሎት የመስጠት ተልዕኮዎችን ይዘው እንደተቋቋሙ ገልጸው ከነዚህ ሶስት ስራዎች መካከል ዩኒቨርሲቲዎች የማህበረሰብ አገልግሎት ስራን አቅማቸው በፈቀደ መጠን ያላቸውን የተማረ የሰው ሐይል በማስተባበር እና ማህበረሰቡን በማሳተፍ በጋራ እንደሚያካሂዱት ተናግረዋል ፡፡

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲም በማህበረሰብ አገልግሎት ዘርፍ የሚሰራውን ስራ አሳታፊና ውጤታማ ለማድረግ እንዲረዳው ባለፈው ዓመት ማህበረሰቡንና ባለድርሻ አካላትን በማወያየት የማህበረሰብ አገልግሎት ስራ የሚመራበት ፍኖተ ካርታ እንደተዘጋጀና በዚህ ፍኖተ ካርታ ላይም በአካባቢው ያሉ የጎሉ ችግሮችን ለመቅረፍና ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶ ሊሰራባቸው የሚገቡ ጉዳዮች ተለይተው በቅደም ተከተል እንደተቀመጡ አስታውሰው በየዓመቱ የሚወጡ ዕቅዶችም ይህንን በጥናት የተዘጋጀ ፍኖተ ካርታ መሰረት ያደረጉ መሆናቸውን ገልጸዋል ፡፡

Haramaya University held a discussion with representatives from the local community regarding the activities it planned to carry out during the year

ከዚህ ጋር ተያይዞ ብዙውን ጊዜ ከግንዛቤ እጥረት የተነሳ ዩኒቨርሲቲው እንደማንኛውም የመንግስት ተቋም በተመደበለት በጀት እንደሚተዳደር በመዘንጋትና ዩኒቨርሲቲውን እንደ እርዳታ ሰጪ ድርጅት በማየት የተለያዩ ጥያቄዎች ይዘው የመምጣት ሁኔታዎች እናዳሉ ጠቅሰው ዩኒቨርሲቲው በተመደበለት በጀት መሰረት ዕቅድ አውጥቶ እንደሚሰራ መገንዘብና በዚሁ ዕቅድ ላይ  በጋራ ተወያይቶና አዳብሮ ተቀናጅቶ መስራት እንደሚገባ አመልክተዋል ፡፡

በዕለቱ በዩኒቨርሲቲው የማህበረሰብ ልማትስራዎች ዳይሬክቶሬት በ2009 ዓ.ም ሊሰሩ የታቀዱ የልማት ስራዎችበዝርዝር ቀርበው ውይይት የተደረገባቸው ሲሆን ከነዚህ ሊሰሩ ከታቀዱ ስራዎች መካከልምርትና ምርታማነትን የሚጨምሩና መሰረተ ልማትን የማያስፋፉ ስራዎች እንዲሁም የስራ ፈጠራንና ቢዝነስ ዲቭሎፕመንትን (ኢንተረፕረነርሸፕ) የማገዝ ስራዎች፣ለጤናአገልግሎት መስፋፋት ድጋፍ ማድረግ፣ተፈጥሮንና አከባቢን የመንከባከብ ስራ፣ጥራቱ የተጠበቀ ትምህርት እንዲስፋፋ መስራት፣ለአቅም ግንባታ ትኩረት መሰጠትና ማህበራዊ ፍትህን የማስፋፋት ስራዎች ይገኙበታል ፡፡

Haramaya University held a discussion with representatives from the local community regarding the activities it planned to carry out during the year

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ ልማት ስራዎች ዳይሬክቶሬትዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር አድማሱ ቦጋለ በምክክር መድረኩ የተደረጉ ውይይቶችንና የተሰነዘሩ ገንቢ ሀሳቦችን አስመልክተው እንደተናገሩት ዩኒቨርሲቲው በማህበረሰብ አገልግሎት ዘርፍ ለመስራት ያቀዳቸውን ስራዎች በአሳታፊነት ከማህበረሰቡና ከሚመለከታቸው ቢሮዎች ጋር በቅንጅት ለመተግበር እንዲቻል መድረኩ ትልቅ አቅም የፈጠረ እንደሆነ ገልጸው ዩኒቨርሲቲው እንደ ከዚህ ቀደሙ ሁሉ የማህበረሰቡን ህይወት ሊያሻሽሉ በሚችሉ የልማት ስረዎች ላይ በትጋት እንደሚሳተፍ ገልጸዋል ፡፡

Haramaya University held a discussion with representatives from the local community regarding the activities it planned to carry out during the year

በምክክር መድረኩ ላይ የተገኙት የሐረማያ ከተማ ከንቲባ አቶ መሀመድ አሊ እንደተናገሩት ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ያደገረጉ በርካታ ስራዎች ሲሰራ እንደቆየና በተለይም በግብርናው ዘርፍ በጥናትና ምርምር የተገኙ ምርጥ ዘሮችን ለገበሬው በማከፋፈልና ቴክኖሎጂውን በማስፋፈት ገበሬውን ተጠቃሚ ያደረገ ሰፊ ስራ መስራቱን ብሎም ከግብርናው ባለፈ  በአቅም ግንባታና በስራ ፈጠራ ላይ በርካታ ስራዎችን መስራቱን ገልጸዋል፡፡ አቶ መሀመድ አያይዘው እንዳሉት ዩኒቨርሲቲው በ2009 ዓ/ም ለመስራት ባቀዳቸው የአቅም ግንባታ፣ የስራ ፈጠራ ፣ የአካባቢ ልማትና ሌሎችም ስራዎች ላይ ውይይት ማድረጋቸውንና የታቀዱት ስራዎችም ለአካባቢው ማህበረሰብ እጅግ አስፈላጊና መሰረታዊ በመሆናቸው ማህበረሰቡን በማስተባበር ከዩኒቨርሲቲው ጋር በጋራ ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

Haramaya University held a discussion with representatives from the local community regarding the activities it planned to carry out during the year

የባቴ ከተማ ነዎሪና የሐገር ሽምግሌ የሆኑት አቶ ጣሀ አብራሂም በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው ወደ ፊት ለማህበረሰቡ የሚሰራውን ስራ በተመለከተ የአካባቢውን ነዋሪ ተወካዮች ጋብዞ ዕቅዱን ማቅረቡ ዩኒቨርሲቲው ምን ለመስራት እንዳቀደ ከማሳወቅ በተጨማሪ ስረዎቹን ተጋግዞ በመስራት ውጤት ለማምጣት እንደሚረዳ ጠቅሰው የታቀዱት ስራዎች ነዋሪውን የሚጠቅሙ በመሆናቸው ዩኒቨርሲቲው ጠንክሮ ስራ ላይ እንዲያውላቸው መልክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

Haramaya University held a discussion with representatives from the local community regarding the activities it planned to carry out during the year

የአወዳይ ከተማ ከንቲባ ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ አብይ ግርማ በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው የአካባቢውን ከተሞች ለማልማትና ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ ከአካባቢው ከተሞች ጋር በጋራ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸው ለአብነትም ዩኒቨርሲቲው ባለፈው ዓመት ለአወዳይ ከተማ የውስጥ መንገድ ስራ የሚውል 1.5 ሚሊየን ብር ድጋፍ አድርጎ የኮብል ስቶን መንገድ እንደተሰራና በአሁኑም ወቅት መንገዱ በዩኒቨርሲቲው ስም ተሰይሞ አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡ በቀጣይ የሚሰሩ የልማት ስራዎችን በተመለከተም በዚህ መልኩ በጋራ ውይይት መደረጉ ጠቃሚ እንደሆነም አክለው ተናግረዋል ፡፡