የሐረሪ ክልል የሴቶች ፣ ህጻትና ወጣቶች ቢሮ በ2009 ዓ.ም በክልሉ ከሚገኙ ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ በመሆን በሴቶችና ህጻናት መብት አጠባበቅ ላይ በስፋት ለመስራት እንዲያስችለው ለሶስት ቀናት ከክልሉ ከተለያዩ ቢሮዎች ለተውጣጡ አርባ አምስት ባለሞያዎች ስልጠና ሰጥቷል ፡፡
ስልጠናው በዋነኛነት በሴቶችና ህጻናት መብቶች ዙሪያ ዓለም አቀፍ ፣ አህጉራዊና አገራዊ የሆኑ ህጎች ድንጋጌዎች መሰረት የተሰጠ ሲሆን ከህጉ አንጻርም በተግባር ያሉ ሁኔታዎች ምን እንደሚመስሉ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተደርጓል ፡፡

Haramaya and Harari Regional State

የስልጠናው ተካፋይ ሲስተር ጸሀይ ወርቅአለማሁ በበኩላቸው እንደተናገሩት ስልጠናው አገራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ህጎች ለሴቶችና ህጻናት የሚሰጡትን መብትና የመንግስት አካላትም መብቶቹን ለማስከበር ያለባቸውን ሀላፊነት በተመለከተ ሰፊ ትምህርት እንዳገኙ ገልጸው ይህን መሰል ስልጠና አስፈጻሚ አካላት በትግበራ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ ለሚሰሩት ስራ አቅም የሚፈጥር በመሆኑ ወደ ፊት ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባው ተናግረዋል ፡፡

Haramaya University and Harari Regional State