በሸምሸዲን መኸመድ ከህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት

መጋቢት 19 ቀን 2007 ዓ.ም በድሬደዋ ስታዲዮም ላይ በተካሄደው የእግር ኳስ ውድድር ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የጤን ቡድን ተጋጣሚውን የድሬደዋ ቀይ መስቀል የጤና ቡድንን 2 ለ 1 በማሸነፍ  ዋንጫ ባለቤት መሆኑ ተገለፀ፡፡

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የውስጥና የውጪ ስፖርት ውድድሮች ደይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ደምመላሽ ተስፋዬ ለየሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የህዝብና ዓለም አቀፍ ደይሬክቶሬት ዘጋቢ እንደገለፁት’የዚህ ስፖርታዊ ውድድር ዋና አላማው አሻናፊና ተሸናፊ ለመለየት ሳይሆን ለታላቁ ህዳሴ ግድባችን ያለንን ፍቅር የለመግለጥና ህዝቡን ይበልጥ ግንዛቤ ለማስጨበጥ ነው” ብለዋል፡፡

Haramaya University won the trophy organized by the Dire Dawa administration in commemoration of the fourth anniversary of the commencement of the Renaissance Dam construction Haramaya University won the trophy organized by the Dire Dawa administration in commemoration of the fourth anniversary of the commencement of the Renaissance Dam construction

አቶ ደምመላሽ እንደተናገሩት የሀረማያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችና ማህበረሰብ ለግድቡ ግንባታ ከቦንድ ግዢ አንስቶ በልዩ ልዩ ተግባራት ተሳትፎ በማድረግ ላይ መሆናቸውን አስረድተው ዳይሬክቶሬቱ ከሚሰራቸው ስራዎች በዋንኝነት የዩኒቨርሲቲውን ተማሪዎች ከቀለም ት/ት በተጨማሪ በስፖርት የዳበረ ጤናማ አካል እንዲኖራቸው እንዲሁም የእርስ በርስ ግንኙነታቸው እንዲዳብርና የተወዳዳሪነት መንፈሳቸው ለማገዝ ነው ብለዋል፡፡

Haramaya University won the trophy organized by the Dire Dawa administration in commemoration of the fourth anniversary of the commencement of the Renaissance Dam constructionHaramaya University won the trophy organized by the Dire Dawa administration in commemoration of the fourth anniversary of the commencement of the Renaissance Dam construction

አያይዘውም ለዚህም ግብ መሳካት የተማሪዎችን የውስጥ ለውስጥ በተለያዩ ስፖርት አይነቶች ውድድር በየዲፓርትመንቶችና በኮሌጆች መካከል በደመቀ ሁኔታ በማካሄድ ላይ መሁኑን ገልጸው ይህም ተግባር ለተማሪዎች ብቻ ሳይሆን ለመምህራንና ለሰራተኞች አስፈላጊ መሆኑን ስላመነበት በኮሌጆች መካከል የእግር ኳስ ውድድር እንዲጀመር ማድረጋቸውን አስረድተዋል ፡፡

በተመሳሳይ መልኩም በፊታችን ቅዳሜ መጋቢት 26 ቀን 2007 ዓ .ም ከጠዋቱ 2፡00 ሰዓት ጀምሮ የታለቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መሠረት የተቀመጠበትን 4ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ በተማሪዎች ቡድንና በጊቢው ማህበረሰብ የጤና ቡድን መካከል የእግር ኳስ እንድሁም ሴት ተመራቂ ተማሪዎች ከ ሴት ተመራቂ ካልሆኑ ተማሪዎች መካከል የገመድ ጉተታ ውድድር እንደሚካሄድ አስረድተው መላው የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብና ተማሪዎች በእለቱ በአሮጌው ስታድዮም በመገኘት ጫወታውን እንዲመለከት ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡