የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የስትራቴጂካዊ አመራርና የተቋማዊለውጥዳይሬክቶሬት ከድሬደዋ የስራአመራርና የካይዘን ኢንስቲቲዩት ጋር በመተባበር በካይዘንአመራርሥርዓትአደረጃጀትዙሪያ ለ120 የካይዘን ልማት ቡድን መሪዎች ስልጠና ሰጠ፡፡

of Haramaya University's Strategic Leadership and Institutional Transformation Directorate, in collaboration with the Dire Dawa Administration and Kaizen Institute, provided training on the Kaizen management system framework.

የዩኒቨርሲቲው ቁልፍ ተግባራት የተሳኩ እንዲሆኑ ከለውጥ መሣሪያዎች አንዱ የሆነውን የካይዘን ሥርዓት ተግባራዊ ለማድረግ ከከፍተኛ አመራር ጀምሮ በተዋረድ ላሉ አካላት ዩኒቨርሲቲው ግንዛቤ የማዳበር ሥራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ የካይዘን አመራር ፍልስፍና ቀጣይነትና ተከታታይነት ያለው የተሻለ ለውጥ በማምጣት ላይ የተመሠረተ ሲሆን ፍልስፍናውም ከሁሉም በላይ የአመለካከት ለውጥ ለማስረፅ የሚያስችል እንደሆነ ይታወቃል፡፡

Haramaya University in collaboration with the Dire Dawa Administration and Kaizen Institute, provided training on the Kaizen management system framework, Professor Nigussie dechassa in the picture

የሀረማያ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝደንት ፕሮፌሰር ንጉሴ ደቻሳ በስልጠናው መክፈቻ ላይ እንደገለጹት የካይዘን አመራር ሥርዓት ለተሻለ ለውጥ፣ ጥራትና ምርታማነት የሚያነሳሳና ለተቋማዊ ለውጥ ድርሻው የጎላ ስለሆነ አመራሩንና ሠራተኛውን በማሳተፍ ተግባራዊ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡

የሥልጠናው ዓላማ የካይዘን ባህሪያትን በመረዳት ከፍተኛው አመራር፣ መካከለኛው አመራር እና ፈጻሚው ሠራተኛ በተደራጀና በተቀናጀ መልክ በመንቀሳቀስ በዩኒቨርሲቲው ፈጣንና ቀጣይነት ያለውን ለውጥ ለማረጋገጥ መሆኑን በስትራቴጂካዊ አመራርና ተቋማዊ ለውጥ ዳይሬክቶሬት የተቋማዊ  ለውጥ ቡድን መሪ ወ/ሮ አበበች ደመላሽ ተናግረዋል፡፡

Haramaya University in collaboration with the Dire Dawa Administration and Kaizen Institute, provided training on the Kaizen management system framework, Professor Nigussie dechassa in the picture, Miss Abebech Demelash in the picture

በዩኒቨርሲቲው የካይዘን ፍልስፍናን ለመተግበር ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የገለፁት ቡደን መሪዋ የካይዘን ዕውቀትና አሰራሮችን በየደረጃው ለማስረፅ የሚያስችሉ ስልጠናዎችን መስጠት ተቀዳሚ ተግባር በመሆኑ በውስጥ ሠራተኞች መሠረታዊ የካይዘን አሠራር  የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በመስጠት ወደ ትግበራው ተገብቶ ብዙ አበረታች ለውጦችና ውጤቶች መገኘቱን አስረድተዋል፡፡

የለውጥ ሥራዎችን በተደራጀ ሁኔታ ለማስኬድ መሰል የስልጠና ሥርዓት መዘርጋቱ ትልቅ ፋይዳ እንደሚኖረው በመጠቆም የአፈፃፀሙንም ውጤታማነት በተገቢው መንገድ ለመገምገም እንዲቻል በአደረጃጀቱ ላይ ጠንካራ ተግባራት ሊሠሩ እንደሚገባ ተሳታፊዎች ገልጸዋል፡፡