የኢፌድሪ የሠላም ሚኒስቴር ከተለያዩ ተቋማት ለተመረቁ ወጣቶች ‘በጎነት ለአብሮነት’ በሚል መርህ ባዘጋጀው ስልጠና ለመሳተፍ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ለተገኙ ወጣቶች አቀባበልና የስልጠና ማስጀመሪያ መርሀ ግብር በአፍረን ቀሎ አዳራሽ እየተከናወነ ይገኛል…
የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንትና የፕሬዝዳንት ተወካይ የሆኑት ፕሮፌሰር መንግስቱ ኡርጌ ለሰልጣኞቹ ባሥተላለፉት መልዕክት በበጎ ፈቃደኝነት አገልግሎት ለመስጠት አካባቢውንና ማኅበረሰቡን መረዳት የሚያስፈልግ በመሆኑ ሰልጣኞች ማኅበረሰባቸውን በሚገባ ለማወቅ እንዲጥሩ ጥሪ አቅርበዋል።